Thursday, December 19, 2019

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ከ100 ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች አንዷ ሆኑ

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ከ100 ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች አንዷ ሆኑ

ፎርብስ መጽሔት ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴን ከ100 የዓመቱ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች መካከል መርጧቸዋል፡፡ ፕሬዚዳንቷ ከመቶ የዓመቱ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች መካከል የተመረጡ ብቸኛ አፍሪካዊት ናቸው፡፡ ፎርብስ ካወዳደራቸው ሴቶች መካከልም ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ 93ኛ ደረጃን ይዘዋል፡፡
ዓምና ጥቅምት ወር ላይ የመጀመርያ ሴት ፕሬዚዳንት ሆነው የተመረጡት ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ፣ አገራቸውን በዲፕሎማሲው ዘርፍ ለረዥም መታት ያገለገሉ ናቸው፡፡ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶችም በልዩ ልዩ ኃላፊነት ደረጃዎች ሠርተዋል፡፡
አምና ከተመረጡ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች መካከል አፍሪካዊቷ ኢሳቤላ ዶ ሳንቶስ አንዷ ነበሩ፡፡ ኢሳቤላ የቀድሞ የአንጎላ ፕሬዚዳንት ሆዜ ኤድዋርዶ ዶ ሳንቶስ ልጅ እንደሆኑ ፎርብስ አስታውሷል፡፡
የጀርመኗ አንጌላ መርኬል፣ ከፈረንሣይ ክርስቲን ላጋርዴ፣ ከአሜሪካ ናንሲ ፔሎሲ በዓመቱ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች ዝርዝር ውስጥ ቀዳሚ በመሆን ከአንድ እስከ ሦስተኛ ደረጃ ይዘዋል፡፡ ሜሊንዳ ጌትስ ስድስተኛ፣ ኦፕራ ዊንፍሬይ 20ኛ ሆነው ሲመረጡ፣ የአየር ንብረት ጥበቃ ተሟጋቿ የ16 ዓመቷ ታዳጊ ግሬታ ተንበርግ ደግሞ 100ኛ ሆናለች፡፡

No comments:

Post a Comment